በዚህ ክፍል ኢየሱስ ሁለት መሠረታዊ ሃሳቦች ያስቀምጣል፡- የመጀመሪያው እርሱ ሕግን ሊፈጽም እንጂ ሊሽር እንዳልመጣ፣ ሁለተኛው የእርሱ ተከታዮች የሆኑት ጽድቅ በዚያን ዘመን ከነበሩ የሃይማኖት መምህራን ጽድቅ እንደሚበልጥ ነው፡፡ ጌታ ሲናገር ከእርሱ ጋር የመፍትሔው አካል የሚሆን ደቀ መዝሙር ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅና ይህንኑ ትምህርት በተግባር ከሰዎች ሁሉ ጋር ማለትም ከወንድሞችም ሆነ ከወደረኞ