ሕዝቅኤል በጣም አስቸጋሪ በሆነ ጊዜና ቦታ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እንዲያገለግል ተጠራ፡፡ እርሱ በባቢሎን ምድር በባርነት እየሰሩ ለሚገኙ የራሱ ሕዝብ የእግዚአብሔርን መልዕክት አመጣ፡፡ ሕዝቅኤል የጀመረው ታላቅ በሆነ በእግዚአብሔር ራዕይ ሲሆን እርሱ በትክክል የጌታን ክብር አይቷል፡፡ እርሱ ትኩረት ሰጥቶ የሚናገረው ስለመንፈስ ቅዱስን ሥራ ነው - የእርሱ ሕዝብ ባለበት ሁሉ የእግዚአብሔር መገኘት እንደሚሆ