እስራኤል የሄዝቦላህ ዋና መቀመጫ ናት ባለቻት ሊባኖስ ላይ የአየር ድብደባ ማካሄድ ከጀመረች ሁለት ሳምንታት ተቆጠሩ። ከቀናት በፊት ደግሞ እግረኛ ጦር በማስገባት ዘመቻዋን ቀጥላለች። በዚህ ጦርነት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ታዲያ ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎቹን ከሊባኖስ ለማስወጣት ስራ እንደሚጀምር ቢያስታውቅም፣ እስካሁን ከምዝገባ ውጪ የታየ እንቅስቃሴ ባለመኖሩ በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ መውደቃቸውን ኢትዮጵያኖቹ ገልጸዋል።