የሳኦል መለወጥ የመንፈስ ቅዱስ አስደናቂ ኃይል መገለጫ ነው፡፡ የወንጌል ፅኑ ጠላት የሆነውን ሳኦልን እግዚአብሔር ወደ ሐዋርያው ጳውሎስነት ለውጦት የወንጌል ታላቅ መልዕክተኛ አደረገው፡፡ ከእርሱ አዲሱ እምነት የተነሳና ዓለምን በወንጌል ለመድረስ ካለው መሰጠት የተነሳ ጳውሎስ እንደ ፈሪሣዊነቱ የነበረውን ስኬትና ክብር ተወ “ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤