ከምርኮ ምድር ወደ ኢየሩሣሌም ለተመለሱ የመጀመሪያዎቹ ተመላሾች ሐጌ ሰበከላቸው፡፡ ከነበረው ጠላትነት የተነሣ የይሁዳ ሰዎች ቤተ መቅደሱን መሥራት ስላልቻሉ የግል ቤቶቻቸውን መሥራት ቀጠሉ፡፡ “ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ” በማለት ሐጌ ሰበከ፡፡ ሐጌ የእግዚአብሔር ሕዝብ ቅድሚያ መስጠት ያለባቸውን ነገር እንዲያስታውሱ፣ ትክክለኛ ዕይታ እንዲኖራቸው፣ ሥራውን ለመቀጠል እንዲነቃቁና እንዳይፈሩ ይጮኸ ነ