ለአማኞች ጠንካራና በፍቅር የሆነ ግንኙነትን ማበልፀግና መጠበቅ ወሳኝ እንደሆነ ኢየሱስ አስተማረ፡፡ የኢየሱስ የምህረት ባህርይ ያላቸው ሰዎች በተግባር ማሳየት አለባቸው፣ ይህንን አለማድረግ የግል አምልኮአችንን ይጎዳል፡፡ ኢየሱስ “ወንድም” የሚለውን ሰው ማግለል የለብንም፡፡ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ህብረት መመሥረት ከፈለግን ለወንድሞቻችና ለእህቶቻችን ያለን ቁጣና የጥላቻ መንፈስ መታረቅ አለበት፡፡