ትክክለኛ ባህርይ በውስጣቸው ያለ ደቀ መዛሙርት የሚኖሩት በትክክለኛ እሴቶች ነው፡፡ እነርሱ ቅድሚያ የሚሰጡት ነገር የተመሠረተው በዘላለማዊነት ላይ ነው እንጂ በምድራዊ ነገሮች ላይ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ደቀ መዛሙርት በምድር ላይ እንደ ጨውና እንደ ብርሃን ተፅዕኖን የሚያደርጉት፡፡ እንደ ኢየሱስ፣ ባለን ጊዜ በምናደርጋቸው ነገሮች የእኛ እሴቶች ምን እንደ ሆኑ ያስታውቁናል፣ ምን እንደምናስብ፣ ምን ዓይነት ስጋትና ምኞት እንዳለን፣ እና ምን ወይም ማንን እንደምናገለግል፣ ምክንያቱም እግዚአብሔርንና ገንዘብን ማገልገል አንችልም፡፡