“የአፍሪካ አህጉር የበርካታ ሀገር በቀል የምግብ ስርዓቶች ባለቤት ናት። እነዚህ የምግብ ስርዓቶች በእምቅ እውቀት፣ በዘላቂና ዘመን ተሻጋሪ አውዶች የተሞሉ ናቸው'' ሲሉ ሼፍ ፋትማታ ቢንታ ተናግረዋል።
🎙 በዚህ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው ስለአፍሪካ የምግብ ስርዓትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ለመወያየት እንደ ሼፍ ቢንታ ያሉ ሙያተኞችን ጨምሮ በርካታ የዘርፉ ባለሙያዎችና የባህል መሪዎችን ጋብዟቸዋል።