በዕዝራ መሪነት ከባቢሎን ምርኮ የተደረገው የመጀመሪያው መመለስ ቤተ መቅደሱን መልሶ ለመገንባት ነው፡፡ ዕዝራ ለመልካም መሪነት ትልቅ ምሳሌ ነው፡፡ ይህ ምሳሌ እግዚአብሔር እንዴትና ለምን እንደ ዕዝራ አይነቱን ሰዎች እንደሚጠቀም ይገልፃል፡፡ መጽሐፈ ዕዝራ፣ መጽሐፈ ነህምያና መጽሐፈ አስቴር ድህረ - ምርኮ የታሪክ መጻሕፍት በመባል ይታወቃሉ፡፡ መጽሐፈ ዕዝራና መጽሐፈ ነህምያ የእግዚአብሔርን ሥራ በእግዚ