ከአጭሩ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ትልቅ ትምህርትን እንማራለን፡፡ ይሁዳ በወደቀች ጊዜ ኤዶም ደስ ስላለውና ስለፈነደቀ እግዚአብሔር በአብድዩ አማካይነት በኤዶም ላይ የፍርድን መልዕክት አስተላለፈ፡፡ በእስራኤልና በኤዶም መካከል ያለው ጠላትነት፣ ከሁለቱ መንትያ ወንድማማቾች፣ ከያዕቆብና ከኤሳው ዘመን ይጀምራል፡፡ እነዚህ ሁለት ወንድማማቾች እግዚአብሔርን በሚፈልጉና የእርሱን ፈቃድ በሚታዘዙ መንፈሳዊ ሰዎች እና