ከሚገጥመን መንፈሳዊ ውድቀት መነሳት እንድንችል ተስፋን፣ ብርታትንና ፅናትን ሊሰጠን የሚችል ጠቃሚ ትምህርትን ከእስራኤላውያን ታሪክ እንማራለን፡፡ ምንም እንኳን ሕዝቡ በእግዚአብሔር ላይ ቢያመነዝሩም እግዚአብሔር ግን ሕዝቡን በጣም ታግሦ ነበር፡፡ ምንጊዜም የእግዚአብሔር ሥራ እንቅፋት ሲገጥመው እግዚአብሔር ነቢያትን ያስነሳ ነበር፡፡ የነቢያት ዋና ሚና ወይም ተግባር በእግዚአብሔር ሥራ ላይ የተነሳን እንቅ