ሰው፤ መንፈሳዊ፣ የፈጠራ ችሎታ ያለው፣ የሚያስብ፣ ስሜት ያለው እና ከሰዎችና ከአምላኩ ጋር ግንኙነት ማድረግ የሚችል ሆኖ በእግዚአብሔር አምሳያ እንደተፈጠረ ኦሪት ዘፍጥረት ያስተምረናል፡፡ ይህ አምሳያ አዳምና ሔዋን ኃጢአትን በሠሩ ጊዜ ተበላሸ፡፡ ሌሎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚናገሩት ይህ የተበላሸውን ግንኙነት ከቅዱሱ እግዚአብሔር ጋር ለማደስ እየተደረገ ያለውን ጥረት ነው፡፡ እግዚአብሔር በመጀመሪያ