የኢያሱ መጽሐፍ ስለእምነት ማለትም እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለውን ፈቃድ ስለሚወርስ አሸናፊ የሆነ እምነት የሚናገር ነው፡፡ ብዙዎቻችን እንደ እስራኤላውያን እግዚአብሔር ለሁሉም አማኞች ያዘጋጀውን መንፈሳዊ በረከቶችን መለማመድ ያቅተናል፤ እነርሱም፡- ፀሎት፣ መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናትና እግዚአብሔርን ማምለክ ናቸው፡፡ ፀሎትን የራሳችሁ የምታደርጉት ስትፀልዩ፣ ቃሉን የራሳችሁ የምታደርጉት መጽሐፍ ቅዱስን ስታነቡት