የዮሐንስ ወንጌል በብዙ መንገድ ልዩ ነው፡፡ ዓላማዎቹ፣ የአጻጻፍ ስልቱ እና ይዘቱ ከሌሎቹ ወንጌላት ይለያል፡፡ የዮሐንስ ወንጌል የተጻፈው ለማያምኑ ሰዎች ሲሆን ዓላማውም እነርሱን ወደ እምነት ለማምጣት ነው፡፡ ዮሐንስ በእያንዳንዱ ምዕራፍ መሠረታዊ ጥቄዎችን ይመልሳል፡- ለምሳሌ “ኢየሱስ ማነው?”፣ “እምነት ምንድነው?”፣ እና “ሕይወት ምንድነው?”፡፡ እርሱ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የሚያረጋግ