የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የኢትዮ-ቴሌኮምን መደበኛ አክሲዮን ሽያጭ ከጀመረ በኋላ የኩባንያውን ያለፈ ዓመት ገቢ እና ትርፍ በማስላት “ያዋጣል” ወይስ “አያዋጣም” የሚሉ ትንታኔዎች በማኅበራዊ ድረ-ገጾች እና በመገናኛ ብዙኃን እየታዩ ነው። መንግሥት ከመደበኛ አክሲዮኖች ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር (255 ሚሊዮን ዶላር) የማግኘት ዕቅድ ያለው ሲሆን ወደፊት የኢትዮ-ቴሌኮም 45 በመቶ ድርሻ ለውጪ ባለወረቶች ይሸጣል ተብሎ ይጠበቃል። ለመሆኑ ልብ መባል ያለባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? ባለሙያዎችስ ምን ይመክራሉ?