Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 115 episodes available.
April 22, 2026የአውሮፓ ኅብረት የበጀት ድጋፍን ጨምሮ ለኢትዮጵያ 559 ሚሊዮን ዩሮ ለማቅረብ ቃል ገባየአውሮፓ ኅብረት በትግራይ ጦርነት ምክንያት ያቋረጠውን የበጀት ድጋፍ ወደ 140 ሚሊዮን ዩሮ ከፍ አድርጎ እንደሚጀምር አስታውቋል። ለዲጂታል ኢኮኖሚ 150 ሚሊዮን ዩሮ፤ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት፣ ፋይበር ኦፕቲክ ለመዘርጋትና የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ለመጠገን 269 ሚሊዮን ዩሮ ያቀርባል። የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ 130 ሚሊዮን ዩሮ ለዘመን ባንክ እና ለኢትዮጵያ መንግሥት ለማበደር ሥምምነት ተፈራርሟል።...more11minPlay
April 15, 2026በአየር ንብረት ለውጥ የኢትዮጵያ ቡና አብቃይ አካባቢዎች ሲስፋፉ በኮሎምቢያ እና ሖንዱራስ እንደሚቀንስ ጥናት አሳየየአየር ንብረት ለውጥ በኢትዮጵያ ለአረቢካ ቡና በጣም ምቹ የሆነውን አካባቢ አሁን ከሚገኝበት 38% በመቶ በምዕተ-ዓመቱ አጋማሽ ወደ 49% ከፍ ሊያደርገው እንደሚችል አንድ ጥናት አሳይቷል። በሮቦ ባንክ ጥናት መሠረት የዓለም ሙቀት ሲጨምር በኢትዮጵያ ደጋማ አካቢዎችን ቡና አምራች ሊያደርጋቸው ቢችልም ኮሎምቢያ እና ሖንዱራስ ተጎጂ ናቸው። ደጋማ አካባቢዎች ሞቃታማ እየሆኑ ሲሔዱ በቡና አመቺነታቸው ቢጨምርም የዝቅተኛ ወይም ቆላማ አካባቢዎች በአንጻሩ ይቀንሳል።...more12minPlay
April 08, 2026የኢትዮጵያ መንግሥት “ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ” የሚከላከል ደንብ እንዲያወጣ እና የግብር እፎይታ እንዲሰጥ ተጠየቀአምስት ሊትር ዘይት በአሶሳ፣ ደሴ እና መቐለ ከተሞች ከ2,200 እስከ 2,500 ብር እየተሸጠ ነው። የመንግሥት መዋቅሮች የዋጋ ጭማሪዎችን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ ነው። የኢትዮጵያ ሸማቾች መብቶች ተቆርቋሪ ድርጅት “ያልተገቡ የዋጋ ጭማሪዎችን በግልጽ የሚከለክል እና የሚያስቀጣ ልዩ መመሪያ” መንግሥት በአስቸኳይ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርቧል።...more11minPlay
April 01, 2026የኢራን ጦርነት በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ላይ “አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው ይጠበቃል”በኢትዮጵያ የነጭ ናፍጣ አቅርቦት በአማካይ በቀን ከ9.2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4.5 ሚሊየን ሊትር ቀንሷል። ሀገሪቱ የኢራን ጦርነት ሲቀሰቀስ የገዛችውን 180,000 ሜትሪክ ቶን ነዳጅ ማስገባት አልቻለችም። በወር ከ15 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለነዳጅ ለመደጎም መገደዱን የገለጸው መንግሥት ዜጎች “ቅድሚያ የማይሰጣቸው ጉዞዎች እንዲሰርዙ” መክሯል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ የኢራን ጦርነት ያስከተለውን የነዳጅ ቀውስ ለመቋቋም ኢትዮጵያውያን “ቅድሚያ የማይሰጣቸው ጉዞዎች እንዲሰርዙ” መክረዋል።...more12minPlay
March 25, 2026በአማራ ክልል ያለው የነዳጅ ዘይት እጥረትና ድብቅ ገበያነዳጅ ከማደያዎች ውጪ በሊትር ደሴ 350 ብር፣ ኮምቦልቻ 500 ብር ዳባት 900 ብር መሸጡን አሽከርካሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በጎንደር እና ባሕር ዳር በነዳጅ ማደያዎች ለወረፋ ከ2,000 እስከ 10,000 ብር ይከፈላል። በአማራ ክልል የነዳጅ እጥረት እና የዋጋ ለውጥ በግብርና እና በኢንዱስትሪ ምርቶች መሸጫ ላይ ጭማሪ አስከትሏል።...more11minPlay
March 18, 2026የነዳጅ ዋጋ ጨምሮ የቡና ሲቀንስ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብርቱ ፈተና ከፊቱ ተጋርጦበታልበታኅሳስ፣ ጥር እና የካቲት ወራት በኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ነጠላ አሀዝ ሆኖ የተመዘገበው የዋጋ ግሽበት የነዳጅ ዋጋ ሲያሻቅብ ሊባባስ ይችላል። የነዳጅ ዋጋ የናረው ሀገሪቱ በቡና ንግድ በዓለም አቀፍ ገበያ የተጋረጠባትን ፈተና ለመሻገር በምትሞክርበት ወቅት መሆኑ በባለሥልጣናቱ ዘንድ ሌላ ሥጋት የፈጠረ ጉዳይ ነው።...more9minPlay
March 11, 2026የነዳጅ ዋጋ “አስፈሪ በሆነ መልኩ” ሲንር ኢትዮጵያ “የቁጠባ እርምጃዎች” ልትከተል ነውአሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን በገጠሙት ጦርነት የነዳጅ ዋጋ ሲንር የኢትዮጵያ መንግሥት ለቤንዚን እና ለነጭ ናፍጣ በሊትር የሚያደርገው ድጎማ በ44 ብር ገደማ እንደጨመረ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል። ከነዳጅ በተጨማሪ የማዳበሪያ ዋጋ በዓለም ገበያ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በማሳየቱ የኢትዮጵያ ገበሬዎችን ሊፈታተን ይችላል። ጦርነቱ ከመቀስቀሱ በፊት የ50 ኪሎግራም የዩሪያ ከረጢት በኢትዮጵያ ከ12 እስከ 15 ዶላር ይሸጥ ነበር። በዓለም አቀፍ ገበያ የ30% የዋጋ ጭማሪ ሲከሰት በኢትዮጵያ ያለው የችርቻሮ ዋጋ ከ16 እስከ 20 ዶላር ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚገመት የቢዝነስ ደቨሎፕመንት ባለሙያው ኢዶሳ ታመነ ይናገራሉ።...more11minPlay
March 04, 2026እስራኤል እና አሜሪካ ከኢራን የገጠሙት ጦርነት በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር አደረገበዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ እስራኤል እና አሜሪካ ከኢራን ጦርነት ከመግጠማቸው በፊት ከነበረው ዋጋ 12% ገደማ ጨምሮ 82 ዶላር አካባቢ ደርሷል። በቀጠር እና ሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ነዳጅ ማምረቻዎች፤ በሖርሙዝ ወሽመጥ የሚቀዝፉ መርከቦች ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። በሖርሙዝ የመርከቦች ምልልስ በ80% ቀንሷል፤ ወደ 3,200 የሚሆኑ መርከቦች ሥራ ፈተዋል...more12minPlay
February 25, 2026ለኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ የአጋርነት መዋጮ መሰብሰብ ተጀምሯልለኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ የባንክና ቴሌኮም አገልግሎቶችን ጨምሮ በተለያዩ ስልቶች የአጋርነት መዋጮ መሰብሰብ ተጀምሯል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኝ ተቋም ባልደረባ ባለፈው ወር ከደመወዛቸው 0.5% መቆረጡን ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል። ባለሙያዎች እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት የሚሰጡት ርዳታ በመቀነሱ አደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ እንደሚያስፈልግ ቢስማሙም መዋጮው ጫና እንደሚኖረው ተናግረዋል።...more10minPlay
February 18, 2026በኢትዮጵያ ጦርነት ዳግም ሲያንዣብብ የትግራይ ክልል ነዋሪዎችና ኢኮኖሚ ካሁኑ ዳፋው ተጭኗቸዋልበኢትዮጵያ ሌላ ጦርነት ሲያዣብብ በትግራይ ክልል የነዳጅ ምርቶች፣ ጤፍ እና ዘይትን ጨምሮ የምግብ ግብዓቶች በአንድ ሣምንት የዋጋ ጭማሪ ታይቶባቸዋል። በክልሉ ከኤቲኤም ገንዘብ ማግኘት አይቻልም። ባንኮች ደንበኞቻቸው ወጪ የሚያደርጉትን የገንዘብ መጠን ገድበዋል። በክልሉ በተፈጠረ ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ምክንያት ለንግድ እና አገልግሎቶች ክፍያ የሚፈጸመው በሞባይል የገንዘብ ማዘዋወሪያዎች ሆኗል።...more12minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 115 episodes available.