Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 125 episodes available.
July 15, 2026የኢትዮጵያ መንግሥት ባንኮች ከሚሰጡት ብድር የተወሰነው ለማምረቻ ዘርፍ እንዲመደብ የሚያስገድድ ሕግ እንዳያወጣ ተመከረየኢትዮጵያ መንግሥት ባንኮች ከሚሰጡት ብድር የተወሰነውን ለማምረቻ ዘርፍ እንዲመድቡ የሚያስገድድ ሕግ ለማውጣት የያዘው ዕቅድ በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ባለሙያዎች ተቃውሞ ገጥሞታል። በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየው የብድር ገደብ መነሳቱ ግን ባንኮች ለአምራቹ ዘርፍ የተሻለ ብድር እንዲሰጡ ዕድል እንደሚፈጥር የብሔራዊ ባንክ ገዢ ተናግረዋል። ባለፈው ሰኞ ይፋ በተደረገው ውሳኔ በ24 በመቶ ተገድቦ የነበረው የባንኮች ብድር ዕድገት ሙሉ በሙሉ የተነሳ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ የወለድ ተመን ወደ 16% ከፍ ብሏል።...more11minPlay
July 08, 2026የግል ባንኮች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይውጣ ለተባለበት የወርቅ ግብይት ዝግጁ ናቸው?ባለፈው ዓመት 3.4 ቢሊዮን ዶላር የነበረው የወርቅ የወጪ ንግድ ዘንድሮ 5.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ባለሥልጣናቱ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በብቸኝነት ከተቆጣጠረው ገበያ እንዲወጣ አይኤምኤፍ ግፊት እያደረገ ነው። የግል ባንኮች የወርቅ ግብይትን ለማካሔድ የሚያስችል የባለሙያ፣ የጥሬ ገንዘብ እና የመሠረተ-ልማት እጥረት አለባቸው።...more13minPlay
July 01, 2026የዐቢይ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ “መጥፎ” በተባለ ሥምምነት ወደ ንግድ ብድር ሊመለስ ነው?ውድ ወለድ የሚከፈልባቸው የንግድ ብድሮች እንዳቆሙ በተደጋጋሚ ምለው የሚገዘቱት የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቃላቸው የሚፈተንበት ሥምምነት ከቦንድ ባለቤቶች ጋር አድርገዋል። ሥምምነቱ ኢትዮጵያ እስከ 9% ወለድ የሚከፈልበት ቦንድ እንድታወጣ የሚያደርግ ነው። ኢትዮጵያ ቦንዱን ካላወጣች ለግል አበዳሪዎቿ እስከ 90 ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ትገደዳለች።...more12minPlay
June 24, 2026“የኢትዮጵያ ዕዳ አሁን ዘላቂ ነው” የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝየብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ የኢትዮጵያ የዕዳ ጫና “ዘላቂ” ወደሚባልነት ደረጃ ዝቅ እንዳለ ተናግረዋል። ዶክተር ኢዮብ የዕዳ ጫናው መቃለሉን የገለጹት ለአከፋፈል ሽግሽግ የሚካሔደው ድርድር ሳይጠናቀቅ ነው። በድርድሩ የሚፈጸሙ የሁለትዮሽ ሥምምነቶች ሲተገበሩ ኢትዮጵያ የሁለት ዓመት ዕዳ በአንድ በጀት ዓመት ልትከፍል እንደምትችል የገንዘብ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ አሕመድ ሽዴ ከፍተኛ አማካሪ ገልጸዋል።...more12minPlay
June 17, 2026ኢትዮጵያ በ2019 ነዳጅ ለመሸመት 6 ቢሊዮን ዶላር ታወጣለች ተብሎ ይጠበቃልየኢትዮጵያ መንግሥት በሚቀጥለው ዓመት ነዳጅ ለመሸመት 6 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ሊያደርግ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል። መንግሥት በዓመቱ በኤክሳይዝ ታክስ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ከነዳጅ 235.6 ቢሊዮን ብር ገደማ መሰብሰብ ይፈልጋል። ለሚቀጥለው ዓመት የተዘጋጀው በጀት ለነዳጅ ድጎማ 20 ቢሊዮን ብር መታቀዱን አሳይቷል።...more10minPlay
June 10, 2026ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለኢትዮጵያ ከፈቀደው ብድር 200 ሚሊዮን ዶላር አስቀድሞ ሊለቅ ነውአሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን የገጠሙት ጦርነት ያሳደረውን ተጽዕኖ ኢትዮጵያ እንድትቋቋም አይኤምኤፍ (IMF) ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ከፈቀደው ብድር ውስጥ 200 ሚሊዮን ዶላር አስቀድሞ እንዲለቀቅ ታቅዷል። ገንዘቡ የተራዘመ ብድር አቅርቦት መርሐ-ግብር አምስተኛ ግምገማ ሲጸድቅ ከሚለቀቀው 468 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ የሚካተት ነው።...more11minPlay
June 03, 2026የሥራ እጥነት እና የመፍትሄ እርምጃዎች በኢትዮጵያከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ወጣት ኢትዮጵያውያን ዲግሪ ይዘው ሥራ ማግኘት ቸግሯቸዋል። ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኬሚካል ምህንድስና የተመረቀችው ወጣት ሥራ ሲጠፋ "ይኸን ሁሉ አመት ባላቃጠልኩ" ለማለት በቅታለች።...more9minPlay
May 20, 2026ኢትዮጵያ 60 ሚሊዮን ገደማ ዜጎቿ ኃይል ሳያገኙ ለጎረቤቶቿ ለምን ትሸጣለች?ታላቁን የህዳሴ ግድብ፣ የአሰላ እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን በተከታታይ ያስመረቀችው ኢትዮጵያ ለኬንያ የምትሸጠውን ኤሌክትሪክ ለማሳደግ እያጤነች ትገኛለች። አራት ተማሪ ልጆቻቸው ትምህርታቸውን በኩራዝ የሚያጠኑትን እናት ጨምሮ 60 ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያን ግን የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙበትን ቀን ይናፍቃሉ።...more10minPlay
May 13, 2026ባይናንስ ከአርብ ጀምሮ በኢትዮጵያ ብር የሚደረግ ግብይት ያቆማልበዓለም ትልቁ የክሪፕቶከረንሲ መገበያያ የሆነው ባይናንስ ከመጪው አርብ ጀምሮ በብር የሚደረጉ ግብይቶች እንደሚያቆም አስታውቋል። ባይናንስ በዘረጋው የመገበያያ መድረክ ከኢትዮጵያ የሚሳተፉት ክሪፕቶከረንሲ “አዋጭ ኢንቨስትመንት” እንደሆነ የሚያምኑ ወጣቶች ናቸው። መሰል ግብይቶች ግን ለሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ተመራጭ እየሆኑ መጥተዋል።...more13minPlay
May 06, 2026የኢትዮጵያ መንግሥት የስድስት ወራት የሀገር ውስጥ ብድር ወለድ ክፍያ ካለፈው ዓመት ሲነጻጸር 250% ጨመረየኢትዮጵያ መንግሥት የ2018 የመጀመሪያ መንፈቅ የሀገር ውስጥ ብድር ወለድ ክፍያ 126.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው ሰነድ አሳይቷል። የወለድ ክፍያው በስድስት ወራት ለዕዳ ከተመደበው በጀት 64.6% ድርሻ አለው። ካለፈው ዓመት ተመሣሣይ ወቅት አኳያ ሲነጻጸር ግን ከ250 በመቶ በላይ ጨምሯል። በ2017 የመጀመሪያ ስድስት ወራት ለሀገር ውስጥ ወለድ መንግሥት 36 ቢሊዮን ብር ከፍሎ ነበር።...more11minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 125 episodes available.