Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 128 episodes available.
August 05, 2026የኢትዮጵያ ብር የምንዛሪ ተመን ከዶላር አኳያ በዓመት 15 በመቶ ተዳክሟልየኢትዮጵያ ብር ባለፈው አንድ ዓመት ብቻ ከዶላር አኳያ ያለው የምንዛሪ ተመን 15 በመቶ ተዳክሟል። በሐምሌ 2016 ተግባራዊ የተደረገው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓት ለውጥ ወርቅና ቡናን የመሳሰሉ ሸቀጦችን የወጪ ንግድ እንዳበረታታ ቢታመንም ሸማቾችን በኃይል የጎዳ ነው። ከዚያ ባሻገር በመደበኛ እና ትይዩ የውጭ ምንዛሪ ገበያዎች መካከል ያለው የተመን ልዩነት አሁንም በሚጠበቀው ልክ አልጠበበም።...more11minPlay
July 29, 2026የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ኩባንያዎች በካፒታል ገበያ እንዲመዘግቡ ግፊት እያደረጉ ነውየኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ሥራ ከጀመረ ከ18 ወራት በኋላ ባለሥልጣናቱ ኩባንያዎች ድርሻዎቻቸውን እንዲያስመዘገቡ እየጎተጎቱ ነው። እስካሁን ስድስት ኩባንያዎች ድርሻዎቻቸውን በሁለተኛው ገበያ ያስመዘገቡ ሲሆን አምስቱ የግል ባንኮች ናቸው።...more10minPlay
July 22, 2026የባሕረ ሰላጤው ሃገራት አፍሪካ ውስጥ በቢሊዮን ዶላሮች መዋዕለ-ንዋይ የሚያፈሱት ለምንድነው?ሀብታሞቹ የባሕረ ሰላጤው ሃገራት በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት መዋዕለ ንዋይ በአፍሪካ በማፍሰስ ላይ ናቸው። የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችና ሳዑዲ አረቢያን የመሳሰሉት ሃገራት የአፍሪካን ገበያ ሲያማትሩ ማሳካት የሚፈልጓቸው አላማዎች ግን የተለያዩ ናቸው። የዶይቸ ቬለው ኬርስተን ክኒፕ ያጠናቀረው ዘገባ ለባሕረ ሰላጤው ሃገራት መዋዕለ-ንዋይ መስፋፋት ገፊው ምክንያት ምንድነው? የአፍሪካ ሃገራትስ ምን ይጠቀማሉ? የሚለውን ይፈትሻል።...more11minPlay
July 15, 2026የኢትዮጵያ መንግሥት ባንኮች ከሚሰጡት ብድር የተወሰነው ለማምረቻ ዘርፍ እንዲመደብ የሚያስገድድ ሕግ እንዳያወጣ ተመከረየኢትዮጵያ መንግሥት ባንኮች ከሚሰጡት ብድር የተወሰነውን ለማምረቻ ዘርፍ እንዲመድቡ የሚያስገድድ ሕግ ለማውጣት የያዘው ዕቅድ በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ባለሙያዎች ተቃውሞ ገጥሞታል። በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየው የብድር ገደብ መነሳቱ ግን ባንኮች ለአምራቹ ዘርፍ የተሻለ ብድር እንዲሰጡ ዕድል እንደሚፈጥር የብሔራዊ ባንክ ገዢ ተናግረዋል። ባለፈው ሰኞ ይፋ በተደረገው ውሳኔ በ24 በመቶ ተገድቦ የነበረው የባንኮች ብድር ዕድገት ሙሉ በሙሉ የተነሳ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ የወለድ ተመን ወደ 16% ከፍ ብሏል።...more11minPlay
July 08, 2026የግል ባንኮች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይውጣ ለተባለበት የወርቅ ግብይት ዝግጁ ናቸው?ባለፈው ዓመት 3.4 ቢሊዮን ዶላር የነበረው የወርቅ የወጪ ንግድ ዘንድሮ 5.5 ቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ባለሥልጣናቱ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በብቸኝነት ከተቆጣጠረው ገበያ እንዲወጣ አይኤምኤፍ ግፊት እያደረገ ነው። የግል ባንኮች የወርቅ ግብይትን ለማካሔድ የሚያስችል የባለሙያ፣ የጥሬ ገንዘብ እና የመሠረተ-ልማት እጥረት አለባቸው።...more13minPlay
July 01, 2026የዐቢይ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ “መጥፎ” በተባለ ሥምምነት ወደ ንግድ ብድር ሊመለስ ነው?ውድ ወለድ የሚከፈልባቸው የንግድ ብድሮች እንዳቆሙ በተደጋጋሚ ምለው የሚገዘቱት የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቃላቸው የሚፈተንበት ሥምምነት ከቦንድ ባለቤቶች ጋር አድርገዋል። ሥምምነቱ ኢትዮጵያ እስከ 9% ወለድ የሚከፈልበት ቦንድ እንድታወጣ የሚያደርግ ነው። ኢትዮጵያ ቦንዱን ካላወጣች ለግል አበዳሪዎቿ እስከ 90 ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ትገደዳለች።...more12minPlay
June 24, 2026“የኢትዮጵያ ዕዳ አሁን ዘላቂ ነው” የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝየብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ የኢትዮጵያ የዕዳ ጫና “ዘላቂ” ወደሚባልነት ደረጃ ዝቅ እንዳለ ተናግረዋል። ዶክተር ኢዮብ የዕዳ ጫናው መቃለሉን የገለጹት ለአከፋፈል ሽግሽግ የሚካሔደው ድርድር ሳይጠናቀቅ ነው። በድርድሩ የሚፈጸሙ የሁለትዮሽ ሥምምነቶች ሲተገበሩ ኢትዮጵያ የሁለት ዓመት ዕዳ በአንድ በጀት ዓመት ልትከፍል እንደምትችል የገንዘብ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ አሕመድ ሽዴ ከፍተኛ አማካሪ ገልጸዋል።...more12minPlay
June 17, 2026ኢትዮጵያ በ2019 ነዳጅ ለመሸመት 6 ቢሊዮን ዶላር ታወጣለች ተብሎ ይጠበቃልየኢትዮጵያ መንግሥት በሚቀጥለው ዓመት ነዳጅ ለመሸመት 6 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ሊያደርግ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል። መንግሥት በዓመቱ በኤክሳይዝ ታክስ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ከነዳጅ 235.6 ቢሊዮን ብር ገደማ መሰብሰብ ይፈልጋል። ለሚቀጥለው ዓመት የተዘጋጀው በጀት ለነዳጅ ድጎማ 20 ቢሊዮን ብር መታቀዱን አሳይቷል።...more10minPlay
June 10, 2026ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለኢትዮጵያ ከፈቀደው ብድር 200 ሚሊዮን ዶላር አስቀድሞ ሊለቅ ነውአሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን የገጠሙት ጦርነት ያሳደረውን ተጽዕኖ ኢትዮጵያ እንድትቋቋም አይኤምኤፍ (IMF) ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ከፈቀደው ብድር ውስጥ 200 ሚሊዮን ዶላር አስቀድሞ እንዲለቀቅ ታቅዷል። ገንዘቡ የተራዘመ ብድር አቅርቦት መርሐ-ግብር አምስተኛ ግምገማ ሲጸድቅ ከሚለቀቀው 468 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ የሚካተት ነው።...more11minPlay
June 03, 2026የሥራ እጥነት እና የመፍትሄ እርምጃዎች በኢትዮጵያከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ወጣት ኢትዮጵያውያን ዲግሪ ይዘው ሥራ ማግኘት ቸግሯቸዋል። ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኬሚካል ምህንድስና የተመረቀችው ወጣት ሥራ ሲጠፋ "ይኸን ሁሉ አመት ባላቃጠልኩ" ለማለት በቅታለች።...more9minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 128 episodes available.