Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።... more
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.
October 08, 2025የኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ልማት ፕሮጀክት እንደ ቀደሙት ሙከራዎች ያሰጋል?የኢትዮጵያ መንግሥት በሶማሌ ክልል ያስጀመረውን የነዳጅ ልማት ፕሮጀክት የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር አንድ አንጃ ተቃውሟል። ኦብነግ ፕሮጀክቱ “ምክክር” እንዳልተደረገበት እና ሕዝቡ “ፈቃዱን እንዳልሰጠ” ተችቷል። ከዚህ ቀደም በነዳጅ ፍለጋ ወቅት ከባድ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚያስታውሱ ተመራማሪዎች አዲሱ ፕሮጀክት “ጥንቃቄ” እንደሚሻ ይመክራሉ።...more11minPlay
October 01, 2025ኢትዮጵያ ለቢሊዮን ዶላር ዕዳ ሽግሽግ ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገውን ውይይት ውጤት እየጠበቀች ነውኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በፊት ከግል ባለወረቶች አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶች እና የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ፓሪስ ዉስጥ ውይይት ጀምረዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከግል አበዳሪዎቹ ጋር የሚደረገውን ድርድር ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የተራዘመ የብድር አቅርቦት አራተኛ ግምገማ በፊት የማጠናቀቅ ዕቅድ አለው።...more10minPlay
September 24, 2025የፖለቲካ ኢኮኖሚስቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ የቤት ሥራዎች ምንድናቸው?የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 11ኛ ገዥ እዮብ ተካልኝ የፖለቲካ ኢኮኖሚስት ናቸው። ከገንዘብ ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት በሱዳን ጎዳና ወደሚገኘው አዲሱ ቢሯቸው ሲዛወሩ ብሔራዊ ባንክ በርካታ ሥራዎች ጀምሮ ይጠብቃቸዋል። ሹመታቸው አነጋጋሪ የመሆኑን ያህል እዮብ በብሔራዊ ባንክ ገዥነታቸው የሚያሳልፏቸው ውሳኔዎችም በዐይነ ቁራኛ የሚታዩ ይሆናሉ።...more11minPlay
September 17, 2025ዘምዘም ባንክ የተከፈለ ካፒታሉን አምስት ቢሊዮን ብር ለማድረስ ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ አክሲዮኖች እየሸጠ ነውበኢትዮጵያ የመጀመሪያው ከወለድ ነጻ ባንክ የሆነው ዘምዘም ባንክ የተከፈለ ካፒታሉን አምስት ቢሊዮን ብር ለማድረስ አክሲዮኖች ለዲያስፖራ እየሸጠ ነው። ባንኩ እስከ መጪው ሰኔ ወር ድረስ ሁለት ቢሊዮን ብር ገደማ ማሰባሰብ ይኖርበታል። የሸሪአ መርህ የሚከተሉ ባንኮች፣ አጠቃላይ ሐብታቸው፣ ተቀማጭ እና የደንበኞቻቸው ቁጥር ቢጨምርም በተጠበቀው ልክ ለማደግ መፍትሔ የሚሹ ጉዳዮች አሉ...more12minPlay
September 10, 2025በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ማሳደግ ወይስ ለጎረቤት ሀገራት መሸጥ? የቱ ይቀድማል?ኬንያ እና ደቡብ ሱዳን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከሚያመነጨው ኃይል መሸመት ይፈልጋሉ። ህዳሴ ኃይል ማመንጨት ከጀመረ ወዲህ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ወደ 54% ከፍ ቢልም የዓለም ባንክ በሐምሌ ይፋ ያደረገው ሰነድ በኢትዮጵያ በገጠር እና የከተማ ዳርቻዎች የሚኖሩ ወደ 71 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደማያገኙ አሳይቷል።...more13minPlay
September 03, 2025“ሰላም ከሌለ ልማት የለም። ልማት ከሌለ ሰላም የለም” የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሲዲ ዑል ታናይጄሪያዊውን አኪንዉሚ አዴሲና የተኩት የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዝደንት ሲዲ ዑል ታ ባለፈው ሰኞ በይፋ ሥራቸውን ጀምረዋል። አዲሱ ፕሬዝደንት የፋይናንስ ሚኒስትሮች እና የብሔራዊ ባንክ ገዥዎችን በሚያካትተው የአፍሪካ ልማት ባንክ አስተዳደር ቦርድ የተመረጡት ግንቦት 21 ቀን 2017 በተካሔደ ምርጫ ነው። የሞሪታኒያው ሰው የሚመሩት አኅጉራዊ ባንክ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሚያስገነባው አቡሴራ አውሮፕላን ማረፊያ 8 ቢሊዮን ዶላር ብድር የማፈላለግ ኃላፊነት ወስዷል።...more12minPlay
August 27, 2025የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሥራ ለመፍጠር ሲያነክስ “ስደት እንደ አማራጭ ሳይሆን እንደ ብቸኛ መፍትሔ እየተቆጠረ ነው”ኢትዮጵያውያን የተሻለ የሥራ እና የገቢ አማራጭ ፍለጋ ወደ አረብ ሀገራት፣ ደቡብ አፍሪካ እና በሰሐራ በኩል ወደ አውሮፓ ሲጓዙ ለሞት፣ ስቃይ እና እንግልት ይዳረጋሉ። ዜናውን የሰሙ አለፍ ሲልም ሰቆቃውን የሚያውቁ ከመሰደድ አልተቆጠቡም። ተማራማሪዎች በኢትዮጵያ “ስደት እንደ አማራጭ ሳይሆን እንደ ብቸኛ መፍትሔ እየተቆጠረ” መምጣቱን ይናገራሉ።...more14minPlay
August 20, 2025የኢትዮጵያ መንግሥት በ160 ቢሊዮን ብር ደመወዝ ሊያሻሽል መሆኑን ሲያሳውቅ ሠራተኞች የዋጋ ጭማሪ አስግቷቸዋልየመንግሥት ሠራተኞች ከመስከረም 2018 ጀምሮ ይደረጋል የተባለው የደመወዝ ጭማሪ እጃቸው ከመግባቱ በፊት የሸቀጦች ዋጋ እና የመኖሪያ ቤት ኪራይ በመሳሰሉት ላይ ጭማሪ ሊያስከትል እንደሚችል ሥጋታቸውን ተናግረዋል። የደመወዝ ጭማሪው 160 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን ተሿሚዎች፣ ተመራጮች፣ የመከላከያ እና የፖሊስ ሠራዊት አባላትን ጨምሮ ለሁሉም የመንግሥት ሠራተኞች የሚደረግ ነው። ደመወዝ ይጨመራል ሲባል “ያልተገባ” የዋጋ ጭማሪ ሊኖር እንደሚችል ያመኑት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ መንግሥት እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።...more10minPlay
August 13, 2025የኢትዮጵያ መንግሥት በትራምፕ 10% ታሪፍ ላይ ከአሜሪካ እንዲደራደር ባለሙያዎች መከሩየዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ የጣለው 10% ታሪፍ ከነሐሴ 01 ቀን 2017 ጀምሮ ሥራ ላይ ውሏል። የኢትዮጵያ ሸቀጦች ወደ አሜሪካ ሲገቡ የሚከፈለው ቀረጥ “ከሌሎች ሀገሮች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ቢሆንም ጉዳቱ በጣም ከፍተኛ” ይሆናል የሚሉ ባለሙያዎች መንግሥት ከዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር እንዲደራደር መክረዋል። ይሁናን ዝቅተኛው ቀረጥ 50% ታሪፍ የተጣለባት የሕንድ ኩባንያዎች ኢትዮጵያን እንዲያማትሩ አድርጓል።...more12minPlay
August 06, 2025የብሔራዊ ባንክ ገዥ በትይዩ የውጪ ምንዛሪ ገበያ የሚንቀሳቀስ ገንዘብ እንደሚወረስ አስጠነቀቁየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከአሜሪካ እና ከዱባይ የሚዘወሩትን ጨምሮ በውጪ ምንዛሪ ትይዩ ገበያ ላይ ዘመቻ ጀምሯል። ባንኩ ከፍተኛ ልዩነት የሚታይባቸው ይፋዊ እና ትይዩ ተመኖች ተዋህደው ወጥ የውጪ ምንዛሪ ገበያ እንዲፈጠር ይፈልጋል። ነጋዴዎችን ጨምሮ ኢ-መደበኛውን ገበያ ለሚጠቀሙ ገንዘባቸው ሊወረስ እንደሚችል የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ አስጠንቅቀዋል።...more11minPlay
FAQs about ከኤኮኖሚው ዓለም:How many episodes does ከኤኮኖሚው ዓለም have?The podcast currently has 100 episodes available.