• ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሯ አይሻ መሐመድን የመከላከያ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ።
• በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን ላይ የቀረበውን ክስ ዛሬ ያስቻለው ችሎት ተከሳሾች አሁንም በፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ ወሰነ።
• በኪንሻሳ ትናንት በተካሄደው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የውጭ ዜጎች እና ኮንጎዎች ተሳትፈዋል ሲል የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ዛሬ አስታወቀ።
• የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ሶስት የሃማስ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእስር ማዘዣ እንዲጣል የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ICC ዋና አቃቢ ህግ ጠየቁ።