አርዕስተ ዜና
«ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ» ፓርቲ ትግራይ ክልል የሽግግር መንግሥት በአስቸኳይ እንዲመሰረት ጥሪ አቀረበ ።
በአማራ ክልል፤ በዋግ ኸምራ ዞን አስተዳደር በረዶ እና ጎርፍ ብርቱ ጥፋት ማድረሱ ተገለጠ ።
የርስ በርስ ጦርነት ባዳቀቃት ሱዳን ውስጥ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ በርካታ የጦርነት ተፈናቃዮችን ጨምሮ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሕይወት አለፈ ።
አፍጋኒስታንን አናውጦ ከ1,400 በላይ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ብርቱ ርእደ-መሬት «በመቶ ሺህዎች ላይ» ተጽእኖውን እንደሚያሳርፍ ተጠቀሰ ። እስካሁን ቢያንስ 3251 ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱ ተዘግቧል ።