የጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች ያደርግ የነበረውን የዕለቱን በረራ ዛሬ ካቋረጠ በኋላ ስጋት እንዳደረባቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ ። ነዋሪዎች በተለይ ለዶቼ ቬለ እንዳሉት በትግራይ እና በአጎራባች የአማራ ክልል አካባቢዎች ግጭት መቀስቀሱ አሰሳስቧቸዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ ለሶማሊያ የምትልከው የምግብ እርዳታ ላይ የጣለችውን እገዳ እንደምታነሳ አስታወቀች።
የአውሮጳ ኅብረት በ15 የኢራን ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ መጣሉን ዛሬ አስታወቀ። ኅብረቱ ማዕቀብ ከጣለባቸው ውስጥ የአብዮታዊ ዘብ ፈጥኖ ደራሽ ሰራዊት ዋና አዛዦችና ባለሥልጣናት ይገኙበታል።