የመጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው በዋስ እንዲለቀቁ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰጥቶት የነበረውን ውሳኔ ዛሬ ውድቅ አደረገው። የተከ
የእስራኤል ጦር ኃይል የኢራንን የስለላ ጉዳይ ሚንስትር ኢስማኢል ኻቲብን መግደሉን አስታወቀ። ኢራን ግድያዉን አላረጋገጠችም።
የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሪድሪሽ ሜርስ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና እሥራኤል በኢራን ላይ ስለከፈቱት ጦርነት፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለጀርመን አማክራ ቢሆን ኖሮ፣ እርምጃው እንዳይወሰድ እንመክራቸው ነበር ሲሉ አስታወቁ። ሜርስ እንዳሉት ዋሽንግተን ስለጦርነቱ ጀርመንን አላማከረችም።