የሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓም አርዕስተ ዜና
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ሻረ።
የአንጎላ መንግሥት የነዳጅ ዘይት ዋጋ ለመጨመር መወሰኑ በዚህ ሳምንት ባስነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 22 ሰዎች መገደላቸውን አሳወቀ።
ጀርመን ለፍልስጤም የመንግሥትነት ዕዉቅና መሰጠት ያለበት የሁለት መንግስታት መፍትሔ ድርድር ሲያበቃ ነው ብላ እንደምታምን አሳወቀች ።ይሁንና እስራኤል በኃይል የያዘችዉን የፍልስጥም ግዛት ለመጠቅላል የእስራኤል ሁለት ሚንስትሮች ያሰሙት ዛቻ የተናጥጠል የዕዉቅና እርምጃ እንድትወስድ ሊያደርጋት እንደሚችል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።