የግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
በተለያዩ መጋዘኖች ውስጥ የተከማቸ ከ60 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የዩናይትድ ስቴትስ የምግብ እርዳታ እየተበላሸ ነው ሲሉ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ተናገሩ።
የዩክሬንና ሩስያ ተወካዮች ዛሬ ኢስታንቡል ቱርክ ውስጥ ያካሄዱት ቀጥተኛ ንግግር በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ከፍተኛ የሚባል ውጤት አለማምጣቱን የዩክሬን ምንጮች አስታውቀዋል።ሩስያ ግን በሰላም ንግግሩ ረክቻለው አለች።
እስራኤል ዛሬ በጋዛ ሰርጥ ባካሄደችው የአየር ድብደባ ቢያንስ 100 ሰዎች ተገድለዋል ሲል የፍልስጤም ዜና አገልግሎት አስታወቀ ። በርካቶች በፍርስራሾች ስር ተቀብረዋል ብሏል።