በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ትናንት በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ አንዲት እናትና ሁለት ልጆቻቸው አስከሬን ተገኘ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን ሳዮ ኖሌ በተባለ ወረዳ ሦስት ሰዎች ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፈጸመ የፖሊስ አባል የሞት ቅጣት ተወሰነበት።
ዩጋንዳ ሕገወጥ ስደተኞችን ከዩናይትድ ስቴትስ ለመቀበል አለመስማማቷን የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣን አስታወቁ።
ጦርነት ባመሳቀላት ሱዳን የዳርፉር ግዛት ሆስፒታል በታጠቁ ግለሰቦች በተፈጸመ ጥቃት 1 ሰው መገደሉንና አገልግሎቱን ማቋረጡን ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን አስታወቀ።
ሩሲያ እሷን ያገለለ የዩክሬን ደኅንነት ውይይት የትም አይደርስም አለች።