• በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ዳግም ባገረሸ የታጣቂዎች ጥቃት ሶስት የጸጥታ ኃይሎችን ጨምሮ 7 ሰዎች ተገደሉ።
• በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በታጣቂዎች እየተፈጸሙ ያሉ ግድያዎች እና ግፎችን ለማስቆም የኦሮሚያ ክልል እና የፌዴራል መንግስቱ ተጨባጭ ርምጃዎችን እንዲወስድ ኢሰመኮ አሳሰበ ።
• ደቡባዊ ጂቡቲ ውስጥ በደረሰ ፍንዳታ አራት ህጻናት መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ። አንድ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድን ግን ህጻናቱ በድሮን ጥቃት መገደላቸውን ገልጿል።
• ኢራን ከባህረ ሰላጤው ሃገራት በተጨማሪ የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ሃገራት የተሻገረ የሚሳኤል ጥቃት መሰንዘሯ ተሰማ።