*የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ዛሬ እሁድ በፖርት ሱዳን ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የሱዳን ብሔራዊ ጦር ቃል አቀባይ ተናገሩ።
*የየመን ሁቲ አማጺያን በዓለም አቀፉ የቴል አቪቭ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ እስራኤል ከፍተኛ የአፀፋ እርምጃ እንደምትወስድ ገለፀች።
*የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምን ያህል የሀገሪቱን ህገ መንግሥት የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው ርግጠኛ እንዳልሆኑ ተናገሩ።
*ኢትዮጵያውያኑ ለሚ ብርሃኑ እና ብርቱካን ወልዴ በቼክ ሪፑብሊክ ዋና ከተማ ፕራግ ዛሬ የተካሄደውን የማራቶን ውድድር በየዘርፋቸው አሸነፉ