የሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
ሊቢያ ውስጥ በወሮበሎች ተይዘው ሲሰቃዩ የነበሩ ከ100 በላይ ስደተኞች ነጻ መውጣታቸውን ሊቢያ አስታወቀች።ከመካከላቸው 5 ሴቶች ይገኙባቸዋል።
የአውሮጳ ኅብረት ከዋሽንግተን ጋር የሚያካሂደው የታሪፍ ንግግር ክልተሳካ 72 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጡ የአሜሪካን ምርቶች የታሪፍ ጭማሪ ዒላማ ሊሆኑ እንደሚችሉ አስጠነቀቀ።
ባለፉት ሁለት ወራት ስፔን ውስጥ ከፍተኛ ሙቀት 1,180 ሰዎችን መግደሉን የሀገሪቱ የአካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ። እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዳለው ከሟቾቹ አብዛኛዎቹ እድሜያቸው ከ65 ዓመት በላይ ነው። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች ናቸው።