ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትግራይ ጦርነት ወቅት ከመንግሥታቸው ወግኖ የተዋጋው የኤርትራ ጦር በአክሱም ከተማ “ወጣቶች በጅምላ” እንደረሸነ ለመጀመሪያ ጊዜ አመኑ። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባሕር ዳር ከተማ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሐኪም የነበሩት ዶክተር አንዱዓለም ዳኜ ገዳይ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ወሰነ። የሱዳን ጦር በመሐመድ ሐምዳን ደጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እና አጋሮቹ በካዱግሊ ከተማ ላይ ያደረጉትን ከበባ ሰበረ። ሩሲያ ለሊቱን በዩክሬን ላይ ከፍተኛ ጥቃት እንደፈጸመች ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ አስታወቁ።