የመጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም.ዐርእስተ ዜና
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግሥት በክልል ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት የሚደነግገውን አዋጅ ዛሬ አሻሻለ ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሥልጣን ዘመን ለተጨማሪ ዓመት እንዲራዘም የሚያስችለው አዋጅ በ2 ድምጸ ተዐቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
ዩናናይትድ ስቴትስ በየመን የጀመረችውን የአየር ጥቃት አጠናክራ በቀጠለችበት በአሁኑ ጊዜ የየመን ሁቲዎች አማጺ ቡድን ሌላ የአሜሪካን ድሮን ጥለናል ሲል ዛሬ አስታወቀ።
በምያንማሩ የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር የሀገሪቱ ወታደራዊ መሪዎች ዛሬ እንደተናገሩት ወደ 2ሺህ 719 ከፍ ብሏል።