በያዝነው ዓመት የዩናይትድ ስቴትስ እርዳታ መቋረጥ ከሀገራቸው የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር በእጥፍ እንዲጨምር ያደርጋል ሲል አንድ የረድኤት ድርጅት አስጠነቀቀ።
ጋዛ ውስጥ እርዳታ ለማከፋፈል የተዘረጋው በዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል የሚደገፈው ተቋም ሲቪሎችን ለሞትና ጉዳት እያጋለጠነው በማለት 171 የረድኤት ድርጅቶች እንዲቋረጥ ጠየቁ።
በጀርመኗ ሜልሪች ሽታት ከተማ አንድ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ ሠራተኛ ባልደረቦቹ ላይ በባደረሰው ጥቃት የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ ሌሎች ሁለቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደረሰ።
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የገባችበትን ጦርነት ለማስቆም የሚደረገውን የሰላም ውይይት በማጓተት የቀረበባትን ወቀሳ ውድቅ አደረገች።