ኢትዮጵያ ውስጥ "ፌደራል ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ" የተባለ አዲስ የፖለቲካ ድርጅት በምሥረታ ላይ መሆኑን ፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ ዛሬ ለዶቼ ቬለ ተናገሩ።
በኢራን በአገር አቀፍ ደረጃ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ መንግሥት ማብረዱን አስታወቀ።
ለቀናት ከዘለቀ ውጊያ በኋላ የሶሪያ ጦር አሌፖን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ።
የኩርድ ተወካዮች ግን ይህን አጣጥለው ውጊያው ቀጥሏል ብለዋል።
የጋዛ ሰርጥ ነዋሪዎች ሁኔታ በዚህ በክረምት ወቅት ይበልጥ መባባሱን የጀርመን ቀይ መስቀል ድርጅት አስታወቀ።
ሩሲያ እና ዩክሬን ሌሊቱን አንዳቸው ሌላቸው ላይ የድሮን ጥቃቶች ሰነዘሩ
የጂ7 ጉባኤ ለትራምፕ ልደት ሲባል አንድ ቀን ተገፋ።