አርስተ ዜና፤
--የጀርመኑ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዛሬ ዩክሪን መዲና ኪይቭን ሲጎበኙ ሃገራቸዉ ጀርመን ከዩክሬን ጎን በመቆም ዩክሬን እራሷን መከላከል እንድትችል በዘመናዊ የአየር መከላከያን ጨምሮ የሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዕርዳታ እንደምታደር ገለፁ። --እስራኤል በሰሜናዊ ጋዛ እጅግ አስከፊ የቦንብ ድብደባ መፈፀሟ ተገለፀ ። የተኩስ አቁም ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት፤ እስራኤል ፍልስጤማዉያን ሰሜናዊ ጋዛን ለቀዉ እንዲወጡ ጠይቃለች። --በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ትናንት በደረሰ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ የሰዎች ህይወት ጠፋ።--በተለያዩ የአዉሮጳ ክፍሎች ከፍተኛ የአየር ሙቀት ተከሰተ።