የሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
ከመላ ኢትዮጵያ፣ በሕገወጥ መንገድ በመተማ ዮሐንስ በኩል፣ ወደ ሱዳን የሚሰደዱ ወጣቶችና ህፃናት ቁጥር በእጅጉ እየጨመረ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስታወቀ። በዞኑ የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ እንዳለውበተለይ ከትግራይ ክልል የሚሰደዱት ቁጥር ከፈተኛ ነው።
ምያንማር ውስጥ አሁንም በአጋቾች እንደተያዙ ነው የተባሉ 42 ኢትዮጵያውን እጣ ፈንታ አለመታወቁን በምያንማር የተጎጂ ወጣቶች ቤተሰቦች አስተባባሪ ለዶቼቬለ ተናገሩ።
ዋሽንግተን ያሸማገለቻቸው የኮንጎ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክና ሩዋንዳ ዛሬ ዋሽንግተን ውስጥ የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።