-የኢትዮጵያ መንግስት የሥራ ሁኔታ እንዲሻሻልላቸዉ የጠየቁ የሕክምና ባለሙያዎችን ማሠርና ማዋካቡን እንዲያቆም ሑዩማን ራይትስ ዋች ጠየቀ።ዓለም አቀፉ የሠብአዊ መብት ተሟጋች እንድርጅት እንደሚለዉ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ለጥያቄዉ ተገቢ መልስ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎቹን ያስራሉ፣ያዋክባሉ፣ ማሕበራቸዉን ያግዳሉም።---የኬንያ ፀጥታ አስከባሪዎች ትናንት አደባባይ በወጡ ተቃዉሞ ሰልፈኞች ላይ በወሰዱት የኃይል ርምጃ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 16 ደረሰ።ከ400 በላይ ቆስለዋል።--የእስራኤል-የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናትና የኢራን ጠላቶቻቸዉ የገጠሙት የቃላት ዉዝግብ እንቀጠለ ነዉ።ሶሥቱም በየፊናቸዉ ድል እድርገናል ይላሉ።