ጋምቤላ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት የሰላም ጉባኤዎች እየተካሄዱ ነው።
ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ የአሜሪካ ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ የሚያግድ ደንብ ይፋ አደረጉ። የትራምፕ አስተዳደር የሁለቱን ጨምሮ ወደ 40 ገደማ ሃገራት ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ በቅርቡ አግዷል።
ተርክዬ እራሱን እስላማዊ መንግሥት የሚለው በእንግሊዝና ምህጻሩ IS በተባለው ቡድን አባልነት የተጠረጠሩ 125 ሰዎች አሠረች። በዘመቻው እስካሁን የታሰሩት 600 ደርሰዋል።
የአውሮጳ ሕብረት እስራኤል ጋዛ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የረድኤት ድርጅቶችን ማገዷ ሕይወት አድን እርዳታዎች ወደ ሕዝቡ እንዳይደርሱ ያደርጋል ሲል አስጠነቀቀ።