የዓለም ዜና

የዓለም ዜና፤ ሰኔ 17 ቀን፣ 2017 ማክሰኞ


Listen Later

--ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሰዋል ሲሉ ወቀሱ። በሌላ በኩል ኢራን የኒኩሊየር ተቋሞችዋን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆንዋን አስታዉቃለች።--የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት የ(ኔቶ) መሪዎች ኔዘርላንድስ ላይ ታሪካዊ የተባለዉን የሁለት ቀናት ጉባኤ ጀመሩ። 32 የዓለም ሃገራት አባላት የሆኑበት የዓለም ትልቁ የደህንነት ድርጅት ለደህንነት ተጨማሪ ወጭ ለማዉጣት ይስማማሉ አልያም ያለስምምነት ይበተናሉ ተብሎ ይጠበቃል።--በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡኔ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም በሚኖሩ መነኮሳት ላይ በተፈጸመ ጥቃት የአንድ መናኝ ህይወት ጠፋ፤ አንድ አባት ጉዳት ደርሰባቸዉ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW