--ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሰዋል ሲሉ ወቀሱ። በሌላ በኩል ኢራን የኒኩሊየር ተቋሞችዋን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆንዋን አስታዉቃለች።--የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት የ(ኔቶ) መሪዎች ኔዘርላንድስ ላይ ታሪካዊ የተባለዉን የሁለት ቀናት ጉባኤ ጀመሩ። 32 የዓለም ሃገራት አባላት የሆኑበት የዓለም ትልቁ የደህንነት ድርጅት ለደህንነት ተጨማሪ ወጭ ለማዉጣት ይስማማሉ አልያም ያለስምምነት ይበተናሉ ተብሎ ይጠበቃል።--በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡኔ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም በሚኖሩ መነኮሳት ላይ በተፈጸመ ጥቃት የአንድ መናኝ ህይወት ጠፋ፤ አንድ አባት ጉዳት ደርሰባቸዉ።