Sign up to save your podcastsEmail addressPasswordRegisterOrContinue with GoogleAlready have an account? Log in here.
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት... more
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 475 episodes available.
June 04, 2025የግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናየግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜናአንድ የዕቃ ማጓጓዣ አውሮፕላን ዛሬ በሱዳንዋ ምዕራብ ዳርፉር ግዛት ውስጥ በሚገኝ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሰ በቦምብ መመታቱን የዓይን ምስክሮች ተናገሩ። ጋዛ ሰርጥ ውስጥ እርዳታ የሚያከፋፈልባቸው ማዕከላት ለጊዜው መዘጋታቸውን በዩናይትድ ስቴትስና በእስራኤል የሚደገፈው የጋዛ ሰብዓዊ ድርጅት የተባለው ቡድን አስታወቀ። የአውሮፓ ኅብረት ዋነኛ የንግድ ተደራዳሪ ማሮስ ስፌሶቪክ ዩናይትድ ስቴትስ ዛሬ በብረታ ብረቶች ላይ በእጥፍ የታሪፍ ጭማሪ ማድረጓ ድርድሩን የሚያግዝ እንደማይሆን ተናግረዋል።...more11minPlay
June 03, 2025የግንቦት 26 ቀን 2017 የዓለም ዜናየህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ፖለቲከኞች ክልሉን ለዳግም ጦርነት ከሚዳርግ እንቅስቃሴ እንዲታቀቡ የሚደረገዉ ጥሪና ማሳሰቢያ እንደቀጠለ ነዉ።የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታት የገጠሙት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻና የሚያደርጉት ዝግጅት ዳግም ጦርነት ሊገጥሙ ነዉ የሚለዉን ሥጋት እያናረዉ ነዉ።---ለምዕራባዊ ሱዳን ግዛት ለዳፋር ሕዝብ የሚከፋፈል ርዳታ የጫኑ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ካሚዮኖች መደብደባቸዉን ድርጅቱ አስታወቀ።በጥቃቱ ሰዎች ተጎድተዋል።የሱዳን ጦርነት ያሰደደዉ ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከአራት ሚሊዮን በልጧል።-የሩሲያና የዩክሬን ጦር ኃይላት አንዳቸዉ የሌላቸዉን ይዞታ ማጥቃታቸዉን ዛሬም እንደመሰንበቻዉ ቀጥለዉ ዉለዋል።...more12minPlay
June 02, 2025የዓለም ዜና፤ ግንቦት 25 ቀን 2017 ሰኞአርስተ ዜና--- አቶ ታዬ ደንደዓ ከዚህ በፊት ነጻ የተባሉባቸውን የክስ ጭብጦች በመሻር እንዲከላከሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ አዘዘ፡፡ በሌላ በኩል አቶ ታየ ከፍርድ ቤት መልስ መታሰራቸዉ ተሰምቷል።--የቀድሞዋ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ቤርቦክ በኒውዮርክ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆነዉ ተሾሙ።--ሳዑዲ አረቢያ ላልተወሰነ ጊዜ ለኢትዮጵያና ለሌሎች ስድስት የአፍሪቃ ሃገራት ዜጎች የሥራ ቪዛ መስጠት ማቋረጥዋን አስታወቀች።--በሚልዮን የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ከዓመታዊው የሐጅ መንፈሳዊ ጉዞ በፊት ወደ ቅድስት ከተማ መካ እየገቡ ነዉ።...more13minPlay
June 01, 2025የግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ ም የዓለም ዜና*ናይጄሪያ ውስጥ 22 አትሉቶች በአውቶቢስ አደጋ ሞቱ*ህገ ወጥ አፍሪካውያን ስደተኞች ከቲኒዚያ መመለስ ይሻሉ*ዩክሬን ከ 40 በላይ የሩሲያ አይሮፕኖችን አወደምኩ አለች*ኢራን ከአውሮፓ ማዕቀብ ቢጣልባት አጸፋ እንደምትወስድ ዛተች*ከቻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ በኋላ በፈረንሳይ ሁለት ሰዎች ተገደሉ፣ በመቶዎች ታሰሩ...more9minPlay
May 31, 2025የግንቦት 23 ቀን 2017 ዓ ም የዓለም ዜና*ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ አስታወቀ*ፖላንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ በስድስት ሀገራት ህገ ወጥ ስደተኞች ላይ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ጀመረች*በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለውን የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀብ አራዘመ*ናይጄሪያ ውስጥ በጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ 150 አለፈ*የተራቡ ፍልስጤማውያን የርዳታ ምግብ ዘረፉ*ኢራን የተብላለ የዩራንየም ክምችቷን 60 በመቶ አደረሰች...more12minPlay
May 30, 2025የግንቦት 22 ቀን 2017 የዓለም ዜናከአዲስ አበባና ከሌሎች የመሐል ኢትዮጵያ ግዛቶች ሸቀጦች ጭነዉ ወደ ትግራይ ይጓዙ የነበሩ የጭነት መኪኖች አፋርና አማራ ክልል በሚገኙ የፍተሻ ጣቢያዎች መታገዳቸዉን ሾፌሮች አስታወቁ።---የአሜሪካዉ አዉሮፕላን አምራች ኩባንያ ቦይንግ ኢንዶኔዢያና ኢትዮጵያ ዉስጥ በደረሱ አደጋዎች ሰበብ የተመሠረተበት ክስ ሊነሳለት ነዉ።ክሱ የሚነሳዉ ቦይንግ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል በመስማማቱ ነዉ።-እስራኤል ለጋዛ ሕዝብ ሰብአዊ ርዳታ እንዳይደርስ ማገዷን እንድታቆም የሚደረግባት ግፊት እንደቀጠለ ነዉ።የእስራኤል መከላከያ ሚንስትር ግን መንግሥታቸዉ ምዕራባዊ ዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የአይሁዳዊ የእስራኤል መንግሥት እንደሚመሠርት ዝተዋል።...more12minPlay
May 29, 2025የግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ ም የዓለም ዜና*የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢሳያስ አፈወርቂ ወቀሳ ላይ ምላሽ ሰጠ*የግብፁ ፕሬዚዳንት አልሲሲ ብርቱ ተፎካካሪ ከስር ተፈቱ* ናይጄሪያ ውስጥ በሁለት አመታት ውስጥ ከ 10 000 በላይ ሰዎች ተገደሉ*«እስራኤል በጋዛ የጦር ወንጀል እየፈፀመች ነው» የቀድሞ የእስራኤል ጠ/ሚነስትር*ኤሎን ማስክ ለትራምፕ መስራታቸውን ሊያቆሙ ነው*የዩናይትድ ስቴትስ ለአለም አቀፍ ተማሪዎች ቪዛ ላለመስጠት መወሰኗ ቁጣ ቀሰቀሰ...more11minPlay
May 28, 2025የግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናየደርግ ሥርዓት ከኢትዮጵያ የመንግሥት ሥልጣን ከተወገደ ዛሬ 34 ዓመቱን ደፈነ። ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በብሔራዊ በዓልነት ይታሰብ የነበረው ግንቦት 20 በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች መደበኛ የሥራ ቀን ሆኖ ሲያልፍ ትግራይ ክልል ግን በደመቀ ሥርዓት ተከብሯል። ፖርት ሱዳንን ጨምሮ በሱዳን ጦር ኃይል የተያዙ አካባቢዎች ላይ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት መፈጸሙ ተዘገበ። የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ ዩናይትድ ስቴትስን አስጠነቀቁ። የፈረንሳይ ፍርድ ቤት በአብዛኛው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕጻናትን ጨምሮ ወደ 300 ገደማ ህሙማን ላይ በደል በፈጸመ የቀዶ ህክምና ባለሙያ ላይ የ20 ዓመት እስራት ፈረደ።...more10minPlay
May 27, 2025የዓለም ዜና፤ ግንቦት 19 ቀን 2017አርስተ ዜና የጀርመኑ መራሔ መንግሥት ፍሬድሪክ ሜርስ ስራኤል በጋዛ እየፈፀመች ያለዉ ድርጊት «ትክክል ያልሆነ» ሲሉ ወቀሱ። በሌላ በኩል ጀርመንን ጨምሮ ቁልፍ ምዕራባዉያን የዩክሪን ደጋፊዎች ለዩክሪን በሚልኩት የጦር መሳርያ ላይ የተጣለ ገደብን አነሱ።--በእነአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ግዚያዊ የምዝገባ ፍቃድ አገኘ።--በጦርነት በተመሰቃቀለችዉ ሱዳን በኮሌራ በሽታ የተያዘዉ ሰዉ ቁጥር መጨመሩን የጤና ጥበቃ ሚ/ር አስታወቀ።--የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላኖች የፊንላንድ የአየር ክልልን ጥሰዋል ከተባለ በኋላ ፊንላንድ የሩሲያን አምባሳደር ለጥያቄ ጠራች።...more12minPlay
May 26, 2025የግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜናበጋምቤላ ክልል ዲማ ወረዳ ታጣቂዎች በአንድ አውቶብስ ላይ ባደረሱት ጥቃት አምስት ሰዎች ተገደሉ። ሌሎች ስድስት ሰዎችም ተጎድተዋል። ጥቃት አድራሾቹ ከደቡብ ሱዳን የመጡ የሙርሌ ታጣቂዎች መሆናቸው ተገልጿል።የግሪክ ባሕር ኃይል ከ500 በላይ ስደተኞችን ከመስመጥ ማዳኑን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ገለጹ።ዩጋንዳ ከጀርመን ጋር መከላከያን በተመለከተ ያላትን ትብብር ማቋረጧን አስታወቀች። የእስራኤል መንግሥት በቅርቡ ጋዛ ላይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ተነገረ። ሃገራት እስራኤል ጋዛ ላይ የምትወስደውን የኃይል እርምጃ እንድታቆም እየጠየቁ ነው።...more9minPlay
FAQs about የዓለም ዜና:How many episodes does የዓለም ዜና have?The podcast currently has 475 episodes available.