አርስተ ዜና---
አቶ ታዬ ደንደዓ ከዚህ በፊት ነጻ የተባሉባቸውን የክስ ጭብጦች በመሻር እንዲከላከሉ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ አዘዘ፡፡ በሌላ በኩል አቶ ታየ ከፍርድ ቤት መልስ መታሰራቸዉ ተሰምቷል።--የቀድሞዋ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ቤርቦክ በኒውዮርክ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆነዉ ተሾሙ።--ሳዑዲ አረቢያ ላልተወሰነ ጊዜ ለኢትዮጵያና ለሌሎች ስድስት የአፍሪቃ ሃገራት ዜጎች የሥራ ቪዛ መስጠት ማቋረጥዋን አስታወቀች።--በሚልዮን የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ከዓመታዊው የሐጅ መንፈሳዊ ጉዞ በፊት ወደ ቅድስት ከተማ መካ እየገቡ ነዉ።