በናይጄሪያ አንዲት ሴት አጥፍቶ ጠፊ በፈጸመችው የቦምብ ጥቃት 20 የጸረ እስላማዊ ጀሃድ ታጣቂዎች መገደላቸውን ተሰማ።እስራኤል ኢስፋሃን የሚገኘውን የኢራን የኒኩሌር ማብለያ ተቋም ላይ ጥቃት መፈጸሟን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። እስራኤል በተቋሙ ጥቃት ብትፈፅምም ምንም አይነት ሰዎችን ሊጎዳ የሚችል ኬሚካል አለመፍሰሱን አክለዋል። የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ኢራን የኒኩሌር የጦር መሳሪያ ስለማምረቷ ምንም አይነት ተጨባጭ ማስረጃ እንደሌለ ለእስራኤል ደጋግመን ነግረናታል አሉ።