• የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ተዋጊዎቹ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽመዋል በሚል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያቀረበበትን ክስ አጣጣለ፡፡
• በኬንያ መዲና ናይሮቢ በተከሰተ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ በትንሹ የ23 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።
• የደቡብ ሱዳን ጦር የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይልና ሌሎች ድርጅቶች በአማጽያን ይዞታ ስር ካሉ አካባቢዎች ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ።
• የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በደቡባዊ እና ምሥራቃዊ ሊባኖስ በሚገኙ የሂዝቦላህ የጦር ሰፈሮች ላይ ከፍተኛ የአየር ድብደባ ማድረጉን ዛሬ ቅዳሜ አስታወቀ።