የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች እና አክቲቪስቶች “ጦርነት ይቁም፣ ግፋዊ አገዛዝ ይብቃ፣ ሰላም ይምጣ” የሚል ጥሪ ያቀረቡበትን ትዕይንተ-ሕዝብ በበይነ-መረብ አካሔዱ። በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች “በፖለቲካዊ እና የብሔር ልዩነት ምክንያት የተቀሰቀሰ የትጥቅ ግጭት እየተባባሰ” መሔዱን የአውሮፓ የሲቪል ጥበቃ እና የሰብአዊ ርዳታ ሥራ ክፍል አስታወቀ። በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው ተፈናቀሉ። የእስራኤል ጦር በሰሜናዊ ጋዛ የሚገኙ ነዋሪዎች መንደራቸውን ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጠ። በዩክሬን ኻርካይቭ ላይ ሩሲያ በድሮኖች እና ሚሳይሎች በፈጸመችው ጥቃት ሦስት ሰዎች ተገደሉ።