• ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ሲፒ ጄ በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ አምስት ጋዜጠኞች የሽብር ወንጀል ፈጽመናል ብለው አምነው ይቅርታ እንዲጠይቁ የሚደረግባቸውን ግፊት አወገዘ።
• የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በብሄራዊ ጦሩ ላይ መጠነ ሰፊ የአየር እና የምድር ጥቃት መክፈቱን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገበ።
• ዩጋንዳ በሶማሊያ የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ኃይሏን እዚያው እንደምታቆይ አስታወቀች።
• የኢቦላ ወረርሽኝ ኮንጎ ውስጥ ተዋህሲው እስካሁን ባልደረሰበት ግዛት ውስጥ ተከሰተ
• ፈረንሳይ የእስራኤል ሰፋሪዎች በኃይል በተያዘችው የዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የሚፈጽሙትን ጥቃት በይፋ አወገዘች።