በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት የተለያዩ ሰብሎችና አትክልቶችን ለጉዳት መዳረጉን ነዋሪዎች እና የዞኑ አስተዳደር ለዶቼቬለ ተናገሩ።
በዴሞክራቲክ ኮንጎ ምሥራቃዊ ግዛት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ተሐዋሲ ስርጭት መባባሱ ተገለጸ። የሟቾች ቁጥር ከ1,700 በልጧል።
በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጽያን በአንድ ተጨማሪ የሳዑዲ አረብያ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸመቸው ተዘገበ።
ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭና አካባቢው ላይ በሚሳኤል እና በሰው አልባ አውሮፕላኖች ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 17 ሰዎች ተገደሉ፤ ከ40 በላይም ቆሰሉ።