የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሮይተርስ የጋዜጠኖች ቡድን የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ እንዳይዘግቡ ፍቃድ መከልከሉን የዜና ወኪሉ አስታወቀ። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከጥር መጨረሻ ጀምሮ በከባድ የጦር መሣሪያ የታገዘ ግጭት መኖሩን ነዋሪዎች፣ ማኅበራት እና የዞኑ ፖሊስ ገለፁ። የኢራን መንግስት በሰላማዊ በሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን የሐይል እርምጃ የሚመረምር ገለልተኛ አጣሪ ቡድን አቋቋመ። አሜሪካ ሁለተኛዋ ግዙፍ የጦር አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ወደ መካከለኛ ምስራቅ እንደምትልክ ተሰማ።