የዓለም ዜና

DW Amharic የሕዳር 25 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

አቶ ታዬ ደንደአ በፍርድ ቤት በተፈቀደላቸው ዋስትና መሠረት ከእስር ቤት ሲወጡ በጸጥታ ኃይሎች ታፍነው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በአይሱዙ መኪና ላይ በደረሰው ጥቃት ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ወጊያ ሲካሔድ መዋሉን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። ልማት ባንክ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ጨምሮ ስምንት ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥር ተጠቃለሉ። ናሚቢያ ኔቱምቦ ናንዲ ንዳይትዋ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝደንት እንዲሆኑ መረጠች።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW