አቶ ታዬ ደንደአ በፍርድ ቤት በተፈቀደላቸው ዋስትና መሠረት ከእስር ቤት ሲወጡ በጸጥታ ኃይሎች ታፍነው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በአይሱዙ መኪና ላይ በደረሰው ጥቃት ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ወጊያ ሲካሔድ መዋሉን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። ልማት ባንክ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ጨምሮ ስምንት ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥር ተጠቃለሉ። ናሚቢያ ኔቱምቦ ናንዲ ንዳይትዋ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝደንት እንዲሆኑ መረጠች።