ርዋንዳ በሙስና እና ሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም የጠረጠረቻቸውን ሦስት ባለሥልጣናት አሰረች። በኢራን ሻሒድ ራጃኢ ወደብ ላይ በተከሰተ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 40 አሻቀበ። በካናዳ ቫንኮቨር ከተማ በሚኖሩ የፊሊፒንስ ዜጎች መርሐ-ግብር ላይ አንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ ነድቶ ዘጠኝ ሰዎች ገደለ። የእስራኤል ጦር በቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሚኖሩ ሰዎች ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቀ። ሩሲያ የዩክሬን ጦር ሠራዊት፣ የውጪ ተዋጊዎች እና በአውሮፓ የተላኩ ወታደራዊ አሰልጣኞች የሚጠቀሙባቸው ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን እንደምትቀጥል አስታወቀች። በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ ትዕግሥት አሰፋ የዓለም የሴቶች ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፈች