የዓለም ዜና

DW Amharic የሚያዝያ 30 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን አቶ ኤርሚያስ አመልጋን ጨምሮ “በሕገ-ወጥ መንገድ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ለሕዝብ ሽያጭ በማቅረብ ገንዘብ ሲያሰባስቡ ነበር” ተብለው በተጠረጠሩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ምርመራ ጀመረ። የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ቻይና ሠራሽ የጦር መሣሪያዎች ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ማቅረቧን እንዳረጋገጠ አምስነቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። የጀርመን ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር በዩክሬን ጦርነት የምትነዛውን ታሪካዊ ውሸት ነቀፉ። ሩሲያ የድል ቀንን ለመዘከር ስትዘጋጅ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የቻይና አቻቸው ሺ ጂን ፒንግ ለምዕራቡ ያላቸውን እምቢተኝነት በግልጽ አሳይተዋል።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW