የዓለም ዜና

DW Amharic የነሐሴ 9 ቀን 2016 የዓለም ዜና


Listen Later

የጋምቤላ ምክር ቤት ዓለሚቱ ኡሞድን በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት የክልል ፕሬዝደንት አድርጎ ሾመ። ከኢትዮ- ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 32 የጭነት ሎኮሞቲቮች 17ቱ አይሰሩም ተባለ። በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ የግብረ-ሠናይ ሠራተኛ ማንነቱ ባልታወቀ ወንጀለኛ ቡድን ተገደሉ። የ15 ዓመቱ ሔመን በቀለ የታይም መጽሔት የዓመቱ ምርጥ ታዳጊ ተብሎ ተመረጠ። የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት የአድሬ የድንበር መሸጋገሪያን ለሦስት ወራት ሊከፍት ነው። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጦጣ ፈንጣጣ 548 ሰዎች መግደሉ ተገለጸ። በጋዛ ተኩስ ለማስቆም የታቀደው የዶሐ ድርድር ያለ ሐማስ ተሳትፎ ተጀመረ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW