የዓለም ዜና

DW Amharic የሰኔ 2 ቀን 2016 የዓለም ዜና


Listen Later

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጉዳት የደረሰበት በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የሚገኘው አጼ ዮሐንስ አራተኛ ኤርፖርት ሥራ ጀመረ። በሶማሊያ ጋልጋዱድ ግዛት በተፎካካሪ ጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ቢያንስ 45 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 60 መቁሰላቸውን ባለሥልጣን ተናገሩ። እስራኤል አራት ታጋቾች ባስለቀቀችበት እና በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ባካሔደችው ወታደራዊ ዘመቻ የተገደሉ ፍልስጤማውን ቁጥር ወደ 274 ማሻቀቡን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። አውሮፓውያን በአኅጉራዊው ምክር ቤት የሚወክሏቸውን ሕግ አውጪዎች ለመምረጥ ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለሦስተኛ ተከታታይ የሥልጣን ዘመን ቃለ-መሐላ ፈጸሙ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW