የዓለም ዜና

DW Amharic የጥር 17 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

የትግራይ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ከፍተኛ የትግራይ ወታደራዊ መኮንኖች የሰጡትን መግለጫ እና የያዙት አቋም “በመደገፍም ሆነ በመቃወም” ሰልፍ ማካሔድ እንደማይቻል አስታወቀ። ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል 100 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለታንዛኒያ የምትሸጥበት ሥምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በሱዳን ዳርፉር ግዛት ኤል-ፋሽር በሚገኝ ሆስፒታል ላይ በሰው አልባ አውሮፕላን በተፈጸመ ጥቃት 30 ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች ቆሰሉ። ሦስት የደቡብ አፍሪካ ሰላም አስከባሪዎች በዴሞክራቲት ሪፐብሊክ ኮንጎ ተገደሉ። በጋዛ የተኩስ አቁም ሥምምነት መሠረት እስራኤል 200 ፍልስጤማውያን እስረኞችን፤ ሐማስ 4 ታጋቾችን ዛለቀቁ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW