የዓለም ዜና

DW Amharic የኅዳር 27 ቀን 2018 የዓለም ዜና


Listen Later

ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ መካከል “አዲስ ግጭት እንዳይቀሰቀስ መከላከል” ላይ ማተኮር እንዳለባት የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ይፋ ያደረገው የብሔራዊ ደሕንነት ፖሊሲ ሰነድ አሳየ። ኢትዮጵያ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት መስጠት ልትጀምር ነው። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በድሮን በፈጸመው ጥቃት 33 ሕጻናትን ጨምሮ 50 ሰዎች መገደላቸውን የሐኪሞች ቡድን አስታወቀ። በደቡብ አፍሪካ በርካታ ተጠርጣሪዎች በከፈቱት ተኩስ ሕፃናትን ጨምሮ 11 ሰዎች መገደላቸውን ፖሊስ ገለጸ። የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ ወደ እስራኤል እና ዮርዳኖስ አመሩ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW