ያላችሁን ሃሳብ ባመቻችሁ አድራሻዬ አድርሱኝ || email_ [email protected] Telegram @Techforest || Instagram @Yebemuel በቻይናዋ ውሃን ከተማ የኮሮና ቫይረስ ህመም (ኮቪድ ፲፪/ COVID19) ከቁጥጥር ውጭ መሆኑ ከተሰማ ጀምሮ የጤና ጥበቃ ባለሙያዎች በርካታ የሰው ሕይዎትን ለመታደግ የሚረዳ ሙከራዎችን በማድረግ ላይ መሆናቸወን አበክረው ይናገራሉ። በቀርቡ የሳይንስና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ከኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ጋር በመቀናጀት በባህላዊ መንገድ መደሃኒቱን እንዳገኙ ይፋ እድረገዋል። እንደ የአለም የጤና ድርጅት መረጃ WHO World Hello Organisation
የኮሮና ቫይረስ መድኃኒትም ሆነ ክትባት ያልተገኘለት በመሆኑ በቫይረሱ የተጠቁ ህሙማንን መንከባከብ እንጅ በሕክምና ዘዴ መፈወስ አልተቻለም። በመሆኑም ብቸኛው አማራጭ የቫይረሱን ሥርጭት መግታት ነው። የቫይረሱን ሥርጭት ለመግታት ደግሞ መራራቅ፣ እጅን መታጠብ፣ ከቤት መዋል፣ ንፅህናን መጠበቅ ወዘተ ያሉ መንገዶች እንዳሉት በሰፊው የተገለፀ ነው። ግራፉን መዘርጠጥ ማለት እንግዲህ ሁሉንም ዓይነት የጥንቃቄ ዘዴዎች ተጠቅሞ የቫይረሱን ሥርጫት መግታት መቀነስ ነው።.
እስካሁን በቻይና፣ በሰሜን ኮሪያ፣ በጣሊያ፣ በስፔን፣ በኢራን ወዘተ በታየው መሰረት የኮሮናን ቫይረስ ሥርጭት ለመቆጣጠር የሚያችሉትን ዘዴዎች ተግባራዊ ሳይደረጉ ተዘንግቶ የCOVID19 ህሙማን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በ እጥፍ እይጭመረ የመቆጣጠሪያ ዘዴዎቹ በአግባቡ ሰላልተተገበሩ የጤና ጥበቃ ሥርዓቱ ህሙማንን የማስተናገድ አቅሙን እስኪፈታተነው ድረስ ከባድ አደጋ ላይ የወደቁት። በሃገራችን ነባራዊ ሁናቴ በፀና የታመሙ ቁጥራቸው ከፍ ያለ ህሙማን በሆስፒታል ውስጥ ተኝቶ እንክብካቤ የማግኘት ዕድል (Such as use of mechanical ventilator) በበቂ ሊያገኙ ስለማይችሉ ይሞታሉ ማለት ነው። በመሆኑም ተገቢወን ቅድመ ጥነቃቄ መወሰድ የሰዎችን ሕይዎት የማትረፍ ዕድልን ይፈጥራል፣
.በኮሮና ቫይረስ ህመም በአንድ ጊዜ ሊሞቱ የሚችሉ ሰዎችን ቁጥር በመቀነስ በማኅበረሰቡ ውስጥ ሊፈጠር ይችል የነበረውን ድንጋጤ እና ማኅበራዊ ቀውስ ይቀንሳል፣
.በአንድ ጊዜ በበሽታው ሊያዙ የሚችሉ ህሙማንን ቁጥር ይቀንሰዋል። ለጤና ባለሙያዎች የሥራ መደራረብን ይቀንሳል። ይህ ደግሞ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ ትኩረት ህሙማንን እንዲንከባከቡ ዕድል ይሰጣቸዋል፤ በተዘዋዋሪ የጤና ባለሙያዎች በጥድፊያ ሲሰሩ በበሽታው ሊጋለጡ ስለሚችሉ ያንን ዕድልም ያጠበዋል፣
.
ለሕግ አስከባሪዎች እንዲሁም ለሌሎች የመንግሥትና የኅብረተሰብ አካላት የቫይረሱን ሥርጫት ለመቆጣጣር ተጨማሪ ጊዜ ይሰጣቸዋል። አስፈላጊ የሆነ እንደ ጓንት፣ ማስክ ወዘተ ያሉ ዕቃዎችን ለማምረትም ሆነ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ጊዜ ይገዛል፣
.የኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ሥርዓት ደካማ ከመሆኑ አንጻር እና የኅብረተሰባችን የአኗኗር ዘይቤ ማህበራዊ መስተጋቭር ጥግግት የሚዛበት ከመሆኑ አንጻር የተጋረጠወን አደጋ ሊቀንሱ በሚችሉ መንገዶች ላይ ሰፊ ትኩረት አድርጎ መስራት ድርብርብ ጥቅሞች ይኖሩታል ማለት ነው።
.
የጤና ባለሙያዎች እና የመንግሥት አካላት የሚለግሱንን ምክር ተግባራዊ በማድረግ የኮሮናን ቫይረስ ሥርጭት እንግታ።
.
አመሰግናለሁ! እግዚያብሄር ኢትዮጲያነና ህዝቦችዋን ይጠብቅ !
በያለንበት የፈጣሪ ቸር ጥበቃ አይለየን ሰላም ቆዩልኝ !! ይበልጣል ነኝ አዲስ አበባ ኢትዮጲያ የካቲት 21 / 2012