DW Amharic በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንድ ስፔናዊን ጨምሮ አራት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ። የስፔናዊዉ አስክሬን ወደ አዲስ አበባ መላኩ ነዉ የተነገረዉ።- የቀድሞ የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ በሚቀጥለው ሳምንት በሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ ለፓርላማ አባልነት እንዳይወዳደሩ በሀገሪቱ ህገ-መንግስታዊ ፍርድ ቤት ታገዱ።- በሰሜን ምዕራብ ኢራን ታብሪዝ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናዉያን ዛሬ ወደ ጎዳና በመዉጣት ባለፈዉ እሁድ ምሽት በሄሊኮፕተር አደጋ ለሞቱት ለሃገሪቱ ፕሬዚዳንት እና ለሰባት አጃቢ ባለሥልጣናት የሐዘን ሽኝት አደረጉ። ሟቹ ፕሬዚዳንት ሃሙስ ምሽት በትዉልድ ከተማቸዉ የቀብር ስርዓታቸዉ ይፈፀማል።