አርስተ ዜና -የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናት ተባብሶ የቀጠለዉን ጥቁር የውጭ ዜጋ ጥላቻን ተከትሎ ጥቃትን በመፍራት ደርባን በሚገኘ አንድ የቤተክርስቲያን ማእከል ዉስጥ ከለላ የጠየቁ አፍሪቃዉያን ከማዕከሉ አስወጡ። ኢትዮጵያዉያንም ይገኙበታል።-ህንድና የአፍሪቃ ህብረት በሚቀጥለው ሳምንት በኒው ደልሂ ሊያካሂዱት የነበረው የመሪዎች ጉባዔ በኮንጎ በተቀሰቀሰዉ የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ። -የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮ ፈረንሳይ በቅኝ ግዛቶቿ የነበረውን ባርነት ለመቆጣጠር ያገለገሉትን ያረጁ ህግጋቶች እንድታስወግድ እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ሕግጋቱ አገራቸዉ ዛሬ ከምትላቸው እሴቶች ጋር አይጣጣሙም ብለዋል።