አርስተ ዜና፤
--የኩርድ የሠራተኞች ፓርቲ (ፒኬኬ)ቱርክ ዉስጥ ለ 41 ዓመታት ያካሔደውን ደም አፋሳሽ የትጥቅ ትግል ማብቃቱና ቡድኑንም እንደበተነ ፓርቲዉ ዛሬ አስታወቀ።--ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚከፈለን ደመወዝ ተመጣጣኝ አይደለም ሲሉ ሰልፍ የወጡ የጤና ባለሙያዎች ታሰሩ።--በትራምፕ አስተዳደር ፕሮግራም አማካኝነት አሜሪካ ዉስጥ የጥገኝነት መብት የተሰጣቸው ነጭ ደቡብ አፍሪቃውያን የመጀመሪያ ቡድን ደቡብ አፍሪቃን ለቀቁ።--ሀማስ አንድ አሜሪካዊ ታጋችን እንደሚለቅ አስታወቀ።--ጀርመንና እስራኤል የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበት 60ኛ ዓመት ዛሬ በርሊን ላይ ታሰበ።